ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በእውቁ ፖለቲከኛ አንዳርጋቸው ጽጌ ተጽፎ በቅርቡ ለንባብ በበቃው “ትውልድ አይደናገር እኛም እንናገር” መጽሐፍ ላይ በብሔራዊ ቤተመፃሕፍትና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የታሪክ ባለሙያና መምህር የሆኑት ቴዎድሮስ ዘርፉ ሲሆኑ መድረኩ በሰለሞን ተሰማጂ እንደሚመራ ታውቋል፡፡ ፍላጐት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Saturday, 17 August 2019 13:35
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና