Saturday, 31 August 2019 13:39

ስካርሌት ጆሃንሰን በፊልም፣ ቴለር ስዊፍት በሙዚቃ ገቢ ይመራሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ባለፈው አመት የፎርብስ መጽሄት ከፍተኛ ተከፋይ ሴት የፊልም ተዋንያን ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ ላይ የነበረችው ታዋቂዋ የሆሊውድ የፊልም ተዋናይት ስካርሌት ጆሃንሰን፣ ዘንድሮም በ56 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ክብሯን ማስጠበቋ ተነግሯል፡፡ በአመቱ 44.1 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘችው ሌላዋ የፊልም ተዋናይት ሶፍያ ቬርጋራ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ያስታወቀው ፎርብስ፤ ሬሲ ዊዘርስፑን በ35 ሚሊዮን ዶላር ሶስተኛ ደረጃን መያዟን አመልክቷል፡፡
ኒኮል ኪድማን በ34 ሚሊዮን ዶላር፣ ጄኔፈር አኒስተን በ28 ሚሊዮን ዶላር፣ ኬሊ ኩኮ በ25 ሚሊዮን ዶላር፣ ኤልሳቤት ሞስ በ24 ሚሊዮን ዶላር፣ ማርጎት ሪቤ በ23.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ቻሊዜ ቴሮን በ23 ሚሊዮን ዶላር፣ ኤለን ፖምፒዮ በ22 ሚሊዮን ዶላር እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ የፊልም ተዋንያን መሆናቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
በተመሳሳይ መረጃ ደግሞ ቴለር ስዊፍት የአመቱ ከፍተኛ ተከፋይ ሴት ሙዚቀኛ መሆኗንና ድምጻዊቷ ባለፉት 12 ወራት ጊዜ ውስጥ በድምሩ 185 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ፎርብስ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
ቢዮንሴ ኖውልስ 81 ሚሊዮን ዶላር፣ ሪሃና 62 ሚሊዮን ዶላር፣ ኬቲ ፔሪ 57.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ፒንክ 57 ሚሊዮን ዶላር፣ አሪያና ግራንዴ 48 ሚሊዮን ዶላር፣ ጄኔፈር ሎፔዝ 43 ሚሊዮን ዶላር፣ ሌዲ ጋጋ 39.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ሴሌን ዲዮን 37.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ሻኪራ 35 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት እንደ ቅደም ተከተላቸው እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውንም ፎርብስ አስታውቋል፡፡

Read 1361 times