Print this page
Saturday, 31 August 2019 13:41

ባለፉት 8 ወራት በሜዲትራኒያን ባህር የሞቱ ስደተኞች ቁጥር 900 ደርሷል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ባለፈው ሰኞ በሊቢያ የባህር ዳርቻ በደረሰ አደጋ፣ 40 አፍሪካውያን ስደተኞች ለሞት መዳረጋቸውን የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤ ባለፉት ስምንት ወራት ሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት ሲሞክሩ ለሞት የተዳረጉ ስደተኞች   ቁጥር 900 መድረሱን አመልክቷል፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በሊቢያ የባህር ዳርቻ በደረሰው የጀልባ አደጋ 60 ያህል ስደተኞች ከሞት መትረፋቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ አብዛኞቹም የሱዳን፣ የግብጽና የሞሮኮ ዜጎች መሆናቸውን ገልጧል፡፡ ባለፈው ወር በዚያው አካባቢ በደረሰ ተመሳሳይ አደጋ፣ 150 ስደተኞች ለሞት መዳረጋቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ባለፈው አመት ብቻ በሜዲትራኒያን ባህር በደረሱ አደጋዎች ከ2 ሺህ 240 በላይ አፍሪካውያን ስደተኞች የገቡበት ሳይታወቅ መቅረቱን አመልክቷል፡፡

Read 1389 times
Administrator

Latest from Administrator