የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣ የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣ ሀኪም አበበች ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና ተፈጥሮ፣ ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ ደራሲ አለማየሁ ዋሴ (ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::
Saturday, 21 September 2019 12:29
‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የኪነ ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና