Saturday, 21 September 2019 12:29

‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የኪነ ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣ የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣ ሀኪም አበበች ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና ተፈጥሮ፣ ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ ደራሲ አለማየሁ ዋሴ (ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::

Read 1097 times