በጸሐፊ አብዩ ብርሌ (ጌራ) የተዘጋጀውና በኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር እንዲሁም በየካቲት ወረቀት ሥራዎች ድርጅት ትብብር የታተመው
“በሀገር ፍቅር ጉዞ ቅጽ ፩” የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሆቴል ይመረቃል፡፡
ከምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ጎን ለጎን፣ በመጽሐፉ ላይ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌና የሥነ ጽሑፍ ባለሙያው አቶ
መሠረት አበጀ ዳሰሳውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡