Print this page
Tuesday, 01 October 2019 10:55

በግብጽ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች መታሰራቸው ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የግብጽ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ስልጣናቸውን እንዲለቁ የሚጠይቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በመዲናዋ ካይሮ ጣህሪር አደባባይ ባለፈው አርብ የጀመሩት ተቃውሞ ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ፣ የአገሪቱ መንግስት ፖለቲከኞችንና ታዋቂ ግለሰቦችን  ጨምሮ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎችን ማሰሩን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በካይሮ የጀመረው ተቃውሞ በሌሎች ከተሞችም ባለፉት ቀናት ተባብሶ መቀጠሉን የጠቆመው ዘገባው፣ ይህን ተከትሎም ፈቃድ ሳያገኙ ሰልፍ ወጥተዋል በሚል 1 ሺህ 200 ያህል ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አመልክቷል፡፡
ማህበራዊ ድረገጾችን በመጠቀም ተቃውሞ አነሳስተዋል ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ተገናኝተዋል፣ ያለህጋዊ ፈቃድ ሰልፍ ወጥተዋል በሚል ከታሰሩት ግብጻውያን መካከል ሶስት ዝነኛ የፖለቲካ አክቲቪስቶች፣ እውቅ የዩኒቨርሲቲ መምህራን እንደሚገኙበትም ተነግሯል፡፡
ግብጻውያኑ የሰሞኑን ተቃውሞ የጀመሩት ነዋሪነታቸው በስፔን የሆነው ታዋቂው ኮንትራክተርና የፊልም ተዋናይ ሞሃመድ አሊ በቅርቡ የፕሬዚዳንት አልሲሲን ወታደራዊ ሙስና የሚያጋልጡ በርካታ ቪዲዮዎችን በድረገጽ አማካይነት በስፋት ማሰራጨታቸውን ተከትሎ እንደሆነም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 1107 times
Administrator

Latest from Administrator