Saturday, 05 October 2019 00:00

63 ቢ. ዶላር የፈጀው የአለም ግዙፉ አውሮፕላን ማረፊያ በቻይና ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በአለማችን በግዙፍነቱ አቻ እንደማይገኝለት የተነገረውና 63 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት የቻይናው ቤይጂንግ ዳክሲንግ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ  ባለፈው ረቡዕ በይፋ መመረቁን ፎርቹን ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ በተገኙበት በይፋ የተመረቀውና ከመዲናዋ ቤጂንግ በ40 ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሚገኝ 18 ስኩየር ማይል ቦታ ላይ ያረፈው የአለማችን ግዙፉ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ግንባታው አምስት አመታትን ያህል እንደፈጀ ተነግሯል፡፡
98 የእግር ኳስ ሜዳዎችን ያህል ስፋት ያለው ቤይጂንግ ዳክሲንግ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ በመጪዎቹ ሁለት አመታት ጊዜ ውስጥ በድምሩ 45 ሚሊዮን ያህል መንገደኞችን በማስተናገድ ከአለማችን አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያዎች በመስተንግዶ የአንደኛ ደረጃን ለመያዝ ማቀዱንም ዘገባው አመልክቷል፡፡ እጅግ ፈጣኑን 5ጂ ኔትወርክ ጨምሮ በረቀቁ የዘመኑ ቴክኖሎጂዎች እንደተሟላ የተነገረለት አውሮፕላን ማረፊያው፤ በሚያስተናግዳቸው አውሮፕላኖች ቁጥርና በዘመናዊ መስተንግዶውም እጅግ የላቀ እንደሆነ ተገልጧል፡፡


Read 5866 times