Tuesday, 01 October 2019 11:20

በዓመቱ የተለቀቁ ነጠላ ዜማዎች - በዩቲዩብ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 በተሰናበተው የ2011 ዓ.ም በርካታ ትኩረትን የሳቡ ነጠላ ዜማዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የተመለከቷቸውንና ተወዳጆቹን እናስቃኛችሁ::
ከነዚህ መካከል በ“የኛ” የሙዚቃ ቡድን ውስጥ አድጋ “እንደኛ” ወደሚባለው ደረጃ ከተሸጋገሩት አምስት እንስት ድምፃዊያን አንዷና “ምን ልታዘዝ” ተከታታይ ድራማ ላይ ትተውን የነበረችው ድምፃዊት ዘቢባ ግርማ “ገራገር” ነጠላ ዜማ ተወዳጅ ሆኗል፡፡ በተለቀቀ እለት ብቻ 500ሺህ ሰው ያየው ሲሆን፤ እነሆ በአንድ ወሩ ላይ 4.4 ሚሊዮን ሰው ተመልክቶታል:: የሙዚቃ አቀናባሪው ጊልዶ ካሳ ከሁለት ሳምንት በፊት የለቀቀው “ላገባ ነው” አዲስ ነጠላ ዜማ በሁለት ሳምንት ውስጥ 1.5 ሚሊዮን ሰው የመለተው ሲሆን፤ የራሄል ጌቱ “ጥሎብኝ” በ6 ወር አይቶታል፡፡ 10 ሚ. ተመልካች አይቶታል፡፡
በትግርኛ ቋንቋ የተዘፈነው የኤፍሬም አማረ “እሰይ አሰዬ” ነጠላ ዜማም በአንድ ዓመት ውስጥ 18 ሚሊዮን ሰው ሲመለከተው፣ የያሬድ ነጉ “አዲ መራ” በ9 ወር ውስጥ 8.7 ሚሊዮን ተመልካች አግኝቷል:: አሰጌ ዳንዳሾ ከሚካኤል መላኩ (ማይኮ) ጋር በጋራ የተጫወቱት “አኩኩሉ” ነጠላ ዜማ በ3 ወር ውስጥ 3 ሚሊዮን ህዝብ የተመለከተው ሲሆን፤ የሳንቾ “ታናሞ” ዜማ በ5 ወር 2.5 ሚሊዮን ሰው ተመልክቶታል:: የሳራቲ አንድ ነጠላ ዜማ በ10 ወር ውስጥ 3.6 ሚ ተመልካች ያገኘ ሲሆን፤ የዳጊ ዳንኤል “የባሌዋ ቆንጆ” ዘፈን በ4 ወራት ውስጥ 690ሺህ ተመልካች አግኝቷል፡፡ ሮፍናን “ልንገርሽማ” በተሰኘ ዜማው 226ሺ ተመልካች ሲያገኝ ይሁን የተባለው ድምፃዊ በቅርቡ የለቀቀው “ጀማሪ ጀማሪ ነኝ” ዘፈን በሁለት ወር ውስጥ 189 ሺህ ሰው አይቶታል፡፡
በሌላ በኩል፤ በዘንድሮ 10ኛው ዙር “አዲስ ሚዩዚክ አዋርድ” ላይ የኤፍሬም አማረ “እሰይ አሰዬ”፣ የያሬድ ነጉ “አዲመራ እና የራሄል ጌቱ “ጥሎብኝ” ነጠላ ዜማ በምርጥ ነጠላ ዜማ አምስት ውስጥ ዕጩ ሆነዋል፡፡


Read 2421 times