Print this page
Tuesday, 08 October 2019 10:06

ሮቦቶች 200 ሺህ የአሜሪካ የባንክ ሰራተኞችን ከስራ ያፈናቅላሉ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአሜሪካ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ሮቦቶች ሰዎችን በመተካት የሚያከናውኑት ስራ እያደገ መምጣቱንና በመጪዎቹ አስር አመታት ጊዜ ውስጥ በአገሪቱ 200 ሺህ ያህል የባንክ ሰራተኞች ስራ በሮቦቶች ይነጠቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ፎክስ ኒውስ ዘግቧል፡፡
ዌልስ ፋርጎ የተባለ ተቋም የሰራውን ጥናት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ የአሜሪካ ባንኮችና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎታቸውን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና ለሰራተኞች የሚከፍሉትን ወጪ ለመቀነስ በአመት 150 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እያደረጉ ሲሆን ይህም ስራቸውን በሮቦቶች የሚነጠቁ ሰዎች ቁጥር ከፍ እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡
ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰራተኞች ስራዎቻቸውን በሮቦቶች ይነጠቁባቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ የባንክ ክፍሎች መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችና የጥሪ ማዕከሎች ይገኙበታል ያለው ተቋሙ፤ በእነዚህ ክፍሎች ከሚሰሩት ሰራተኞች መካከል 30 በመቶ ያህሉ ስራቸውን እንደሚያጡ አመልክቷል፡፡

Read 1277 times
Administrator

Latest from Administrator