Tuesday, 08 October 2019 10:09

የሊባኖስ ጠ/ሚኒስትር ለደ/አፍሪካዊቷ ሞዴል 16 ሚ. ዶላር ሰጥተዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር አሰድ ሃሪሪ ከአንዲት ደቡብ አፍሪካዊት ሞዴል ጋር የድብቅ የፍቅር ግንኙነት መጀመራቸውንና ከ16 ሚሊዮን ዶላር በላይ በስጦታ መልክ ሰጥተዋል መባሉን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካንዲስ ቫን ደር ሜርዌ ከተባለችው ታዋቂ ደቡብ አፍሪካዊት ሞዴል ጋር ከስድስት አመታት በፊት በሲሸልስ በሚገኝ የመዝናኛ ስፍራ መተዋወቃቸውንና በወቅቱ የ20 አመት ወጣት እንደነበረች ያስታወሰው ዘገባው፤ ከዚያ ጊዜ አንስቶም በድምሩ 16 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ እንደላኩላት መረጋገጡን አመልክቷል፡፡
በፋይናንስና ኢኮኖሚ ቀውስ እየተሰቃየች የምትገኘውን ሊባኖስ በመምራት ላይ የሚገኙት ጠ/ሚኒስትሩ፤ ይሄን ያህል ገንዘብ ለግለሰቧ በስጦታ መልክ ማበርከታቸው ሊደረስበት የቻለው የደቡብ አፍሪካ የግብር መስሪያ ቤት በግለሰቧ ገቢ ላይ ባደረገው ምርመራ ከሊባኖስ ባንክ 16 ሚሊዮን ዶላር እንደተላከላት ማረጋገጡን ተከትሎ እንደሆነም ዘገባው አስታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከገንዘቡ በተጨማሪ እያንዳንዳቸው 250 ሺ ዶላር የሚያወጡ ሁለት የቅንጦት መኪኖችን ለሞዴሏ በስጦታ መልክ ማበርከታቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1633 times