Print this page
Monday, 28 October 2019 00:00

61 በመቶ የዚምባቡዌ ተማሪዎች በክፍያ መናር ትምህርት አቋርጠዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


            በዚምባቡዌ የህዝብ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ ከነበሩት ተማሪዎች መካከል 61 በመቶ ያህሉ የትምህርት ቤት ክፍያቸውን መፈጸም ባለመቻላቸው ሳቢያ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ መገደዳቸው ተዘግቧል፡፡
ምንም እንኳን የአገሪቱ ህግ እያንዳንዱ ዜጋ ትምህርት የማግኘት መብት እንዳለው ቢያረጋግጥም፣ ወላጆች እየናረ ያለውን የትምህርት ቤት ክፍያ ለመፈጸም ባለመቻላቸው፣ ልጆቻቸው ትምህርት ለማቋረጥ መገደዳቸውን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
በትምህርት ቤት ክፍያ መናር ሳቢያ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ በርካታ ህጻናት ከሚገኙባቸው የአገሪቱ አካባቢዎች መካከል  ማታቤሌላንድ የተባለችው ግዛት አንዷ መሆኗን የጠቆመው ዘገባው፤ ሩብ ያህሉ የግዛቲቱ ህጻናት ትምህርት ማቋረጣቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡ በትምህርት ቤት ክፍያ ሳቢያ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ከተገደዱት የዚምባቡዌ ህጻናት መካከል 55 በመቶው ወንዶች መሆናቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 2576 times
Administrator

Latest from Administrator