Tuesday, 29 October 2019 00:00

ኬንያውያን የመንግስት ሰራተኞች የአገራቸውን ልብስ እንዲለብሱ ተገደዱ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

የኬንያ መንግስት፤ የመንግስት ሰራተኞች በሳምንት አንድ ቀንና በህዝባዊ በዓላት በአገር ውስጥ የተመረቱ ልብሶችን ብቻ እንዲለብሱ መመሪያ ማስተላለፉን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት አገር በቀል ኢንዱስትሪዎችን የማበረታታት ዓላማ ያለው ነው የተባለውን ይህንን መመሪያ ለሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤቶች ማሰራጨቱን የጠቆመው ዘገባው፤ መመሪያውን ባላከበሩ የመንግስት ሰራተኞች ላይ ምን አይነት እርምጃ ይወሰዳል የሚለው በግልጽ አለመታወቁን አመልክቷል፡፡
የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታና ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ባለፈው እሁድ በተከበረው የብሔራዊ ጀግኖች በዓል ላይ በአገር ውስጥ የተሰሩ አልባሳትን በመልበስ ለዜጎች ምሳሌ ሆነው ለመታየት መሞከራቸውንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 6800 times