የኬንያ መንግስት፤ የመንግስት ሰራተኞች በሳምንት አንድ ቀንና በህዝባዊ በዓላት በአገር ውስጥ የተመረቱ ልብሶችን ብቻ እንዲለብሱ መመሪያ ማስተላለፉን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት አገር በቀል ኢንዱስትሪዎችን የማበረታታት ዓላማ ያለው ነው የተባለውን ይህንን መመሪያ ለሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤቶች ማሰራጨቱን የጠቆመው ዘገባው፤ መመሪያውን ባላከበሩ የመንግስት ሰራተኞች ላይ ምን አይነት እርምጃ ይወሰዳል የሚለው በግልጽ አለመታወቁን አመልክቷል፡፡
የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታና ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ባለፈው እሁድ በተከበረው የብሔራዊ ጀግኖች በዓል ላይ በአገር ውስጥ የተሰሩ አልባሳትን በመልበስ ለዜጎች ምሳሌ ሆነው ለመታየት መሞከራቸውንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል