‹‹ታመመ ቢሏቸው አንበሳ ባለበት
ሊጠይቁት ሄዱ የምድር ሁሉ አራዊት
ይሄንኑ ሰምታ የጦጣ ብልጣ - ብልጥ
ሳትጠይቀው ቀረች ሳትገባ ወደ ውስጥ
ለምን ብለው ቢሏት መለሰች ጦጢቷ
የገቡት ሳይወጡ ጉዱ ሳይጣራ ቀኑም ሆነ ሌቱ
እንዴት ብዬ እጄን ልስጥ እስከ ማዕሌቱ
አራዊቱ ለአንበሳ ያላቸው ክብር እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ሲታመም እጅግ አሳሰባቸው እንጂ ይሄ ጉልበተኛ በቃ እጁን ይሰጠናል ብለው አሰቡ፡፡ አያ አንበሶ ግን ይብሱን ጉልበት አፈራና ፈረጠመ፡፡ አራዊቱም በጣም ፈሩት፡፡
ከዚያም በሁለት ተከፈሉ፡፡
አንደኞቹ፡-
‹‹ምነው እንዳመመው በዛው በቀሩ››
ከፊሎቹ፡-
‹‹አይ የሚፈራ መሪ ወሳኝ ስለሆነ አያ አንበሶ ያስፈልገናል›› አሉ፡፡
በዚህ አጠቃላይ ግንዛቤ ከብዙ ክርክር በኋላ ተግባቡ፡፡ አያ አንበሶም ሙሉ ለሙሉ አገገመና የዱር አራዊቱን እየተጎማለለ መጎብኘት ጀመረ!
‹‹ታምሜ በመንከባከባችሁ አመሰግናለሁ ትልቅ ውለታ ጥላችሁብኛል!›› አላቸው፡፡
***
አገራችን አንድ መንገድ አጥታለች ወይም ጠፍቶባታል፡፡ ብዙ ሆነን አንድ አገር ማቅናት ዳገት ሆኖብናል፡፡ ማሻሻል አቅቶናል። ለችግሮቿ መፍትሄ አጥተናል፡፡ መንገድም ጠፍቶብናል፡፡
‹‹እንግዲህ ለፍቅር መንገድ አልሰጠውም
ሲገኝ እየጠጣሁ እተኛለሁ የትም›› ማለት ይቀላል፡፡
‹‹ያለፈ ጥረታችንን ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ ያልሞከርነው ነው እሚቆጨኝ›› ማለትም ከሀምሌት ጋር ያዋጣናል፡፡
የሚሰማንን እንጻፍ፡፡ የምንጽፈውም ይሰማልን! በተቻለን ስሜቶቻችንን እንታዘዛቸው፡፡
ዕውነትን ፍለጋ በቆፈርነው ምድር
እህል ዘራንበት በልተን እንድናድር
እንነሳ!
እናብር!
እንተባበር!
እናልም!
እንመንብ!
ክፍተት አንተው!
እንንቀሳቀስ!
እንላወስ!!
Saturday, 02 November 2019 12:39
‹‹አሥራ ስድስቱን ዝንጀሮዎች ባንድ ጥይት ሰፋኋቸው›› ቢለው፤ ‹‹እኔን የገረመኝ ያንተ አገር ዝንጀሮዎች አሰላለፍ ነው!›› አለው
Written by Administrator
Published in
ርዕሰ አንቀፅ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል