Saturday, 02 November 2019 12:48

“ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን” የኪነ ጥበብ ዝግጅት የፊታችን አርብ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)


               በሮያል የማስታወቂያ ድርጅት አዘጋጅነት የሚካሄደውና ራስ መስፍን ስለሺን (አባ ተምትም)ን የሚዘክረው ‹‹ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን›› የተሰኘ የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን አርብ ጥቅምት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት ይካሄዳል፡፡
በእለቱ በእንግድነት የራስ መስፍን ስለሺ ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን በክብር እንግድነት የሚገኙ ሲሆን ሙዚቃ ግጥም ወግና የአርበኛው ሕይወትና ሥራ ታሪክ ለታዳሚ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡
 በጋዜጠኛና ደራሲ ይጥና ደምሴና በጋዜጠኛ ኢዮብ አባተ አስተባባሪነት በሚካሄደው ኪነ ጥበባዊ መሰናዶው ድምፃዊት መሰረት በለጠ፣ በቀለ አረጋ፣ አብነት ደምሴ የክራር ባለሙያዋ የትናየት ይልማ ፍሬዘር ኩራባቸውና ማፊ ልዑል በኢስት አፍሪካ ባንድ ታጅበው የሚያቀነቅኑ ሲሆን፣ ገጣሚያኑ አስታውሰኝ ረጋሳና ትርሲት ሃብተማሪያም ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ መድረክ መሪው አንጋፋው ጋዜጠኛ አባተ ማንደፍሮ ሲሆን መግቢያው ነፃ ነው ተብሏል፡፡


Read 14849 times