Print this page
Monday, 11 November 2019 00:00

ሱዳን የመጀመሪያዋን ሳተላይት ማምጠቋ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ከከፋ የእርስ በእርስ ግጭት ለጥቂት ተርፋ ፊቷን ወደ ሰላም ያዞረችውና በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የምትገኘው ሱዳን፣ የመጀመሪያዋን ሳተላይት ባለፈው እሁድ በተሳካ ሁኔታ ማምጠቋ ተዘግቧል፡፡
የሱዳን ጊዜያዊ መንግስት ምክር ቤት ሃላፊ ጄኔራል አብደል ፈታህ አልቡህራን አገራቸው በቻይና መንግስት በተደረገላት ድጋፍ ወደ ጠፈር ያመጠቀችው ሳተላይት በወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የጠፈር ቴክኖሎጂ ዘርፎች ምርምር ለማድረግ የታለመ መሆኑን መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
“ሱዳን ሪሞት ሴንሲንግ ሳተላይት - ዋን” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሳተላይት፣ ባለፈው እሁድ ማለዳ ከሰሜናዊቷ የቻይና ግዛት ሻንዚ በተሳካ ሁኔታ ወደ ጠፈር መምጠቁን ያስታወሰው ዘገባው፤ ሳተላይቱ እጅግ ጠቃሚ መረጃዎችን በመሰብሰብ ለአገሪቱ ምርምር እድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሎ እንደሚጠበቅ መነገሩንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1563 times
Administrator

Latest from Administrator