የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ ጄፍ ቤዞስ በአሜሪካ ውስጥ ለሚገኙ መኖሪያ ቤት የሌላቸው ዜጎች መርጃ የሚውል 98.5 ሚሊዮን ዶላር መለገሳቸውን ፎርብስ መጽሄት ዘግቧል፡፡የአማዞኑ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጄፍ ቤዞስ፣ በ23 የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ ለሚኖሩ ቤት አልባ ዜጎች መኖሪያ ቤት ለሚሰሩ ድርጅቶች ገንዘቡን መለገሳቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ግለሰቡ ባለፈው አመትም ለተመሳሳይ አላማ 97.5 ሚሊዮን ዶላር በስጦታ ማበርከታቸውን አስታውሷል፡፡