Print this page
Saturday, 30 November 2019 12:33

3.5 በመቶ የአለማችን ህዝብ በስደት ላይ መሆኑ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

      የአለማችን ስደተኞች ቁጥር 272 ሚሊዮን ደርሷል

               በመላው አለም የስደት ህይወትን በመግፋት ላይ የሚገኙ ሰዎች ቁጥር 272 ሚሊዮን መድረሱንና ይህም ከአጠቃላዩ የአለም ህዝብ 3.5 በመቶ ያህሉ ስደተኛ መሆኑን እንደሚያመለክት አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ ከትናንት በስቲያ ባወጣው አመታዊ ሪፖርቱ እንዳለው፤ በርካታ ዜጎቿ የተሰደዱባት ቀዳሚዋ የአለማችን አገር ህንድ ስትሆን፣ 17.5 ሚሊዮን ህንዳውያን የስደት ኑሮን በመግፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ሜክሲኮ በ11.8 ሚሊዮን ስደተኛ ዜጎች በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ 10.7 ሚሊዮን ዜጎች የተሰደዱባት ቻይና በሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደምትቀመጥ አመልክቷል፡፡
በመላው አለም ከሚገኙ 272 ሚሊዮን ስደተኞች መካከል 52 በመቶው ወንዶች መሆናቸውን የጠቆመው አለማቀፉ ሪፖርት፤ የአለማችን ስደተኛ ህጻናት ቁጥርም ከ31 ሚሊዮን በላይ እንደሚሆን ይፋ አድርጓል፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሌሎች አገራት ስደተኞች የሚገኙባት ቀዳሚዋ የአለማችን አገር አሜሪካ መሆኗንና በአገሪቱ 50.7 ሚሊዮን ያህል አለማቀፍ ስደተኞች እንደሚገኙም ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡ በ2018 ስደተኞች ወደ አገራቸው የላኩት ገንዘብ 689 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ህንድ 78.6 ቢሊዮን ዶላር፣ ቻይና 66.4 ቢሊዮን ዶላር፣ ሜክሲኮ 35.7 ቢሊዮን ዶላር ከስደተኞች የተላከላቸው የአለማችን ቀዳሚዎቹ ሶስት አገራት እንደሆኑ አመልክቷል፡፡

Read 1196 times
Administrator

Latest from Administrator