Print this page
Sunday, 08 December 2019 00:00

‹‹ሙዚቃ በያይነቱ›› የሙዚቃ ኮንሰርት ማክሰኞ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

  በጣልያን ባህል ማዕከል አዘጋጅነት የሚካሄደው ‹‹ሙዚቃ በየአይነቱ›› የሙዚቃ ድግስ ማክሰኞ ህዳር 30 ቀን 2012 ከምሽቱ 12፡30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡ ኮንሰርቱ ታዋቂው የጣሊያን የሙዚቃ ባንድ ‹‹ኦርኬስትራ ፒያሳ ቪቶሪያ››፣ የባህል አምባሳደሩ ከያኒ መላኩ በላይና “ኢትዮ ከለር ባንድ” የተጣመሩበት ሲሆን በምሽቱ የተለያዩ የሙዚቃ ተጫዋቾች ስራዎቻቸውን በልዩ ዝግጅት የሚያቀርቡበት ነውም ተብሏል፡፡ በዚህ ኮንሰርት ላይ ለመታደም የመግቢያ ዋጋ የማያስከፍልና በነፃ መዝናናት የሚቻልበትም ነው ተብሏል፡፡

Read 9160 times