የወጣቶቹ ሰዓሊያን ብርሃኑ ዳንኤልና አቤል በየነ ሥራዎች ለእይታ የሚቀርቡበት “ራስ ወዳድነት” የስዕል ኤግዚቢሽን ሰኞ ታህሳስ 6 ቀን 2012 ዓ.ም በፈረንሳይ የባህል ማዕከል (አሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲስ) ከምሽቱ 12፡30 ጀምሮ ይከፈታል፡፡ 35 ያህል የወጣቶቹ ስዕሎች ለዕይታ የሚቀርቡበት ይህ አውደ ርዕይ ተከታታይ 18 ቀናት ለዕይታ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ የተገለፀ ሲሆን፤ የስዕል አድናቂዎች ሥራዎቻቸውን እንዲጐበኙ ሠዓሊዎቹ ጋብዘዋል፡፡