በሕይወት ተረፈ የተጻፈውና ‹‹ምሽቱ ብርሃን›› የተሰኘው መጽሐፍ ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ በዕለቱም የመጽሐፉ ዳሰሳ በፍልስፍና መምህሩ ዮናስ ዘውዴ፣ በጋዜጠኛና ደራሲ ጥበቡ በለጠና በሙዚቃ ባለሞያው ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ይካሄዳል፡፡
ገጣሚያኑ በቃሉ ሙሉ ኤልያስ ሽታሁን መታሰቢያ ታለማ ከባህል የሙዚቃ ቡድን ጋር ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡