Print this page
Saturday, 14 December 2019 12:31

ቴለር ስዊፍት በ185 ሚ. ዶላር ገቢ የአለማችንን ሙዚቀኞች ትመራለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     የአመቱ የጎልደን ግሎብ ሽልማት ዕጩዎች ይፋ ተደረጉ

             ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት በ2019 የፈረንጆች አመት በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ ከፍተኛ ገቢ ያገኙ ዝነኞችን ዝርዝር ከሰሞኑ ይፋ ያደረገ ሲሆን ታዋቂዋ የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ ቴለር ስዊፍት፣ በ185 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
ሌላው ዝነኛ ራፐር ካኔ ዌስት በ150 ሚሊዮን ዶላር የሁለተኛነት ደረጃን ሲይዝ፣ ኤዲ ሼራን በ110 ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ የሶስተኛነት ደረጃ ላይ መቀመጡን ፎርብስ ባወጣው ዘገባው አስታውቋል፡፡
ዘ ኢግልሰ በ100 ሚሊዮን ዶላር፣ ኤልተን ጆን በ84 ሚሊዮን ዶላር፣ ጥንዶቹ ጄይ ዚ እና ቢዮንሴ ኖውልስ እያንዳንዳቸው በ81 ሚሊዮን ዶላር፣ ካናዳዊው ራፐር ድሬክ በ75 ሚሊዮን ዶላር፣ ፒዲዲ በ70 ሚሊዮን ዶላር፣ ሜታሊካ በ68.5 ሚሊዮን ዶላር እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውም ተነግሯል፡፡
በአመቱ ከፍተኛ ገቢ በማግኘት ከአንደኛ እስከ አስረኛ ደረጃን የያዙት ዝነኞች በድምሩ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን የጠቆመው ፎርብስ፤ ይህ ገቢ ባለፈው አመት 866 ሚሊዮን ዶላር እንደነበርም አስታውሷል፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ፣ የ77ኛው የጎልደን ግሎብ የፊልም ሽልማት ዕጩዎች ዝርዝር በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ “ሜሬጅ ስቶሪ” በስድስት ዘርፎች በመታጨት ቀዳሚነቱን መያዙ ተዘግቧል፡፡
ሆሊውድ ፎሪን ፕሬስ አሶሴሽን ባለፈው ሰኞ በካሊፎርኒያ ይፋ ባደረገው የ2020 የጎልደን ግሎብ ሽልማት ዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ በ34 ዘርፎች የታጨችው ሜሪል ስትሪፕ፤ በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽላለች፡፡ የዘንድሮው ጎልደን ግሎብ ሽልማት ስነስርዓት በመጪው ጥር መጀመሪያ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡


Read 1281 times
Administrator

Latest from Administrator