Saturday, 14 December 2019 12:34

የ10 ዶላር መጽሐፍ የሰረቁት የሜክሲኮ አምባሳደር ወደ አገራቸው ተመለሱ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በአርጀንቲና የሜክሲኮ አምባሳደር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትና በቅርቡ ከአንድ መደብር 10 ዶላር የሚያወጣ መጽሐፍ ሲሰርቁ ተይዘዋል የተባሉት ኦስካር ሪካርዶ ቫሌሮ፤ በመንግስት ውሳኔ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የሜክሲኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣውን መግለጫ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ አምባሳደሩ ባለፈው ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ በአርጀንቲና ከሚገኝ አንድ ታዋቂ የመጽሐፍት መደብር፣ የህይወት ታሪክ መጽሐፍ ሲሰርቁ መያዛቸውን የበርካታ መገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑን ተከትሎ፣ ባለፈው ዕሁድ በአፋጣኝ ወደ አገራቸው እንደሚለሱ ተደርጓል፡፡
ቦነሳይረስ ውስጥ ከሚገኘው መደብር መፅሐፉን ሲሰርቁ በጠባቂዎች በቁጥጥር ስር የዋሉትና ለፖሊስ ተላልፈው የተሰጡት የ76 አመቱ አምባሳደር ኦስካር ሪካርዶ ቫሌሮ፤ መጽሐፉን ሲሰርቁ የሚያሳየውና በተለያዩ ማህበራዊ ድረገጾችና መገናኛ ብዙኃን በስፋት እየተሰራጨ የሚገኘው ቪዲዮ እርግጥም ትክክለኛ ሆኖ ከተገኘ፣ የሜክሲኮ የስነምግባር ኮሚቴ፣ በግለሰቡ ላይ የቅጣት እርምጃ ይወስዳል ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው ጠቁሟል፡፡  ግለሰቡ ገንዘብ ሳይከፍሉ የሰረቁት መጽሐፍ በታዋቂው የ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጣሊያናዊ ደራሲ ጂያኮሞ ካሳኖቫ የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2353 times