ሚዩዚክ ሜይ ዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ ‹‹ኢትዮጵያና አባይ›› በተሰኘ ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
በዕለቱ ለውይይቱ ለመነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሑፍ የሚያቀርቡት የ‹‹አይ ምፅዋ›› እና ሌሎች መጻሕፍት ደራሲ የሆኑት ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ ሲሆኑ መርሃ ግብሩን ሰለሞን ተሰማ ጂ እንደሚያጋፍሩት ሚዩዚክ ሜይ ዴይ ገልጾ፣ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ጋብዟል፡፡