በደራሲ ሲሳይ አሰፌ ተሰማ የተሰናዳውና ኮሙዩኒኬሽን ለቢዝነስና አጠቃላይ ህይወት ያለውን ጠቀሜታ እንዲሁም የግንኙነቱ አይነት፣ ጥበብና አተገባበሩ ላይ የሚያጠነጥነው ዳጐስ ያለ መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡
በመጽሐፉ ከግል ጓዳችን እስከ አደባባይ ግንኙነታችን፣ ከፍቅር ጓደኝነት እስከ ስራ አጋርነት፣ ከቤተሰብ አስተዳደር እስከ ድርጅት አመራር፣ ከቢዝነስ አሰራር እስከ ሙያ ስነ - ምግባር ያለውን ሁሉንም የኮሙዩኒኬሽን አይነቶች አካትቶ የያዘና ሁሉም ሰው ሊያነበው የሚገባ ነው ተብሏል፡፡ በ41 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ688 ገጽ የተዘጋጀው መጽሐፉ በ300ብርና በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡