*ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም የመጀመሪያው “አዲስ አድማስ” ጋዜጣ፣ በመጀመሪያው ዕለተ ቅዳሜ ለንባብ በቃ!!
* ላለፉት 20 ዓመታት በየሳምንቱ ቅዳሜ፤ እውነተኛና ትክክለኛ፣ ምሉዕና ሚዛናዊ ዜናዎችን… በመረጃ የበለፀጉ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘገባዎችን…ጠንካራ
ትንታኔዎችን… በኪናዊ ውበታቸው የላቁ ማህበራዊና ጥበባዊ ጽሑፎችን አስነብበናል!!
* አምስት አገራዊ ምርጫዎችን ዘግበን፣ ከአገራችንና ከአንባቢዎቻችን ጋር ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፈናል፤ ለዘንድሮው ምርጫም እየተዘጋጀን ነው!!
*ድንቅ ጽሁፎችን በፍቅር እያበረከታችሁ ለዘለቃችሁ የአድማስ ብዕርተኞች ሁሉ፤ባለውለታዎቻችን ናችሁ!!
* ለሁለት አስርት ዓመታት በፍቅር ያነበባችሁን ሁሉ እናመሰግናለን፤ እንወዳችኋለን!!
*ምርትና አገልግሎታችሁን ለማስተዋወቅ እኛን ለመረጣችሁ ድርጅቶች ሁሉ አክብሮታችንን እንገልጻለን!!
* ዓላማችን መረጃንና ዕውቀትን በማክበር፤ በአዕምሮና በሥራ የሚበለጽግ፣ ራሱን
ችሎ የሚያስብና የሚቆም፣ ምክንያታዊና አስተዋይ ትውልድ ይበረክት ዘንድ መትጋት ነው!!
መልካም የገና በዓል!!!
Published in
ዜና