Monday, 06 January 2020 00:00

በአውሮፕላን አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር በግማሽ መቀነሱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ባለፈው የፈረንጆች አመት 2019 በመላው አለም በአውሮፕላን አደጋ ለሞት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከአንድ አመት በፊት ከነበረው ከግማሽ በላይ ቅናሽ ማሳየቱን ሮይተርስ ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡
ቲ70 የተሰኘውና ተቀማጭነቱ በሆላንድ የሆነው የአቪየሽን ዘርፍ አማካሪ ተቋም ሰሞኑን ያወጣውን አመታዊ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአመቱ በመላው አለም 86 የንግድ አውሮፕላኖች አደጋ እንዳጋጠማቸውና በአደጋዎቹ በድምሩ 257 ሰዎች ለሞት መዳረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአመቱ ለሞት ከተዳረጉት ሰዎች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ድርሻ የሚይዙት ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለሞት የተዳረጉት 157 ሰዎች መሆናቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018 በመላው አለም የተከሰቱት አስከፊ የአውሮፕላን አደጋዎች 13 እንደነበሩና በአደጋዎቹ ለሞት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥርም 534 እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡ የፈረንጆች አመት 2017 በታሪክ እጅግ አነስተኛው የአውሮፕላን አደጋ ክስተት የተመዘገበበት እንደነበር ያስታወሰው ሪፖርቱ፤ በአመቱ የተከሰቱት አስከፊ የአውሮፕላን አደጋዎች ሁለት ብቻ እንደነበሩና የሟቾች ቁጥር 13 ብቻ እንደነበርም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2926 times