Print this page
Saturday, 18 January 2020 13:05

አሜሪካ በወታደራዊ ሃይል ከአለማችን አገራት 1ኛ መሆኗ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   የ2019 የአለማችን አገራት ወታደራዊ ሃይል አቅም ሪፖርት ከሰሞኑ ይፋ የተደረገ ሲሆን 2 ሚሊዮን ያህል የሰው ሃይልና እጅግ ከፍተኛ የጦር መሳሪያ አቅም ያላት አሜሪካ፣ ከአለማችን አገራት በ1ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧ ተነግሯል፡፡
137 የአለማችን አገራት የተካተቱበትንና የሰው ሃይል፣ የጦር መሳሪያ አቅም፣ የኢንዱስትሪ ብቃትና የፋይናንስ አቅምን ጨምሮ የተለያዩ 55 ያህል መስፈርቶችን በመጠቀም በተደረገ ግምገማ፣ ባለፈው ሳምንት ይፋ የተደረገውን የ2019 አለማቀፍ ወታደራዊ አቅም ሪፖርት ጠቅሶ ያሁ ኒውስ እንደዘገበው፤ 716 ቢሊዮን ዶላር የመከላከያ በጀት፣ 13 ሺህ 398 አውሮፕላኖች፣ 2 ሺህ 362 ተዋጊ ጀቶች፣ 6 ሺህ 287 ታንኮችና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎች ያሏት አሜሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች::
በአመቱ የአገራት ወታደራዊ አቅም ደረጃ፣ ሩስያና ቻይና በሁለተኛና በሶስተኛነት ሲከተሉ፤ ህንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን፣ ደቡብ ኮርያ፣ እንግሊዝ፣ ቱርክና ጀርመን እንደ ቅደም ተከተላቸው፣ ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን አገራት መሆናቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 1943 times
Administrator

Latest from Administrator