ሰምና ወርቅ 25ኛው የኪነ ጥበብ ምሽት ‹‹የእኛ ነገር›› በሚል ርዕስ የፊታችን ረቡዕ ጥር 13 ቀን 2012 ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ የፍልስፍና ምሁሩ ዳኛቸው አሰፋ (ዶ/ር)፣ ዲያቆን ቴዎድሮስ በለጠ፣ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ፣ ሙሃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ ፓስተር ካሳሁን ለማ፣ አርቲስትና ጋዜጠኛ ተፈሪ ዓለሙ፣ ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደ (ትዝታችን በኢቢኤስ) ኮሜዲያን ሰመረ ባሪያው፣ ገጣሚያኑ ብሩክ ሚፍታህ፣ ኢዮብ አናጋውና እልፍ ቴዎድሮስ ስራቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን የመግቢያ ዋጋው 100 ብር መሆኑም ታውቋል፡፡