Saturday, 18 January 2020 14:00

የለገር ጥግ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

‹‹ሰጥቼ ገባሁ ለጥቼ ወጣሁ››
አንድ የታወቀ ስመ ጥር ነጋዴ ጉቦ ሰጥተዋል
ተብለው ከበርካታ ግብረ አበሮቻቸው ጋር
እስር ቤት ይገባሉ፡፡ እንደሚታወቀው በእስር
ቤት ዓለም የአንደኛ ተከሳሽ ወንጀል ከሌሎች
አባሪዎቹ ሁሉ የከፋ ተደርጎ ነው የሚወሰደው::
ስለሆነም የመጨረሻው ተከሳሽ ወንጀል
በተነፃፃሪ ሲታይ ቀላል ክስ ነው የሚሆነው፡፡
ከእኒህ ነጋዴ ቀጥሎ ቀላል ክስ አለባቸው
የሚባሉ አንድ ሃያ ሰዎች አሉ፡። ሆኖም ነጋዴው
ተፈቱ፡፡ ነገሩ የገረመው አንድ ሰው ነጋዴውን
አግኝቷቸው፤
‹‹ከእርስዎ ዝቅ ያለና ቀላል ክስ ያለባቸው
ሰዎች እያሉ እርሶ እንዴት ቀድመው ተፈቱ?››
ሲል ጠየቃቸው፡፡
ነጋዴውም፤
‹‹እንግዲህ ምን ይደረግ፡፡ እኔ እንደ መጋዝ
ነው የሆንኩት፡፡ መጋዝ ሲሄድም ይቆርጣል፣
ሲመለስም ይቆርጣል፡፡ ሰጥቼ ገባሁ፤ ሰጥቼ
ወጣሁ!›› ሲሉ መለሱ፡፡
***
እንደ ዛሬው ቋንቋ ቢሆን፤ አባባላቸው፣
በሙስና ገባሁ በሙስና ወጣሁ ይሆን ነበር፤

Read 2988 times