Saturday, 08 February 2020 16:03

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

  ሞልትዋል ብላቴና

ደመረ ብርሃኑ
(በአዲስ አድማስ 15ኛ ዓመት የግጥም
ውድድር 2ኛ የወጣው ግጥም)
ነበር ፍጹም ጨቅላ በጥቁር አፈር ላይ በጥቁር
ተፀንሶ
ጥቁር የወለደው ጥቁር ስጋ አልብሶ፣
ነበር ብላቴና
ከጥቁር ገላ ውስጥ ነጭ ወተት ግቶ
አጥንቱ የጸና የቆመ በርትቶ፣ ነበር ደቀ መዝሙር
ጥቁር ብላቴና
በነጭ ጠመኔ በጥቁር ሰሌዳ
ሀ ሲሉት ሃ ብሎ A ሲሉት A ብሎ
ጥቁሩን ከነጩ ጋር አዋዶ ያጠና፡፡
ታሪክ የጻፈውን ሳይንስ እያጠፋ
ሳይንስ የፃፈውን ሂሳብ እያጠፋ
ሂሳብ የፃፈውን ሲቪኩ እያጠፋ፤
በተዥጎረጎረች ባንዲት ሰሌዳ ላይ
ሁሉም የእየራሱን ሲያስተምር ሲለፋ
አንዲትዋ ሰሌዳ ጥቁር ወዝዋ ወድሞ
ወጭው የጫረውን ገቢው እያጠፋ
ነበር ብላቴና
ካንድ ወንበር ተቀምጦ ትዝብቱ ያልሰፋ
በሰሌዳው ማድያት በስሎ ያልተከፋ፡፡
***

Read 2890 times