Print this page
Saturday, 15 February 2020 11:03

በአባይ ጉዳይ ላይ በሚደረገው ድርድር ኢትዮጵያ ብቻዋን ቆማለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     አሜሪካ፣ አለምባንክ፣ ሱዳን እና ግብጽ ጫና እያሳደሩ ነው
                    በህዳሴው ግድብ ጉዳይ እየተደረገ ባለው ድርድር አሜሪካ፣ አለም ባንክ፣ ግብጽ እና ሱዳን በጋራ ተሰልፈው በኢትዮጵያ ላይ ጫና እየሳረፉ ነው፤ የድርድሩ አቅጣጫም ወደ ውሃ ድርሻ ክፍፍል እንዲዞር ተደርጓል ተብሏል፡፡
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉና በድርድር ሂደቱ ኢትዮጵያን ከወከሉ ኃላፊዎች አንዱ የሆኑ ባለስልጣን ለውጭ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መረጃ ድርድሩ ፈሩን ለቆ ወደ የውሃ ድርሻ ድርድር ዞሯል ብለዋል፡፡
“ቀደም ሲል በግድቡ የውሃ አሞላል ጉዳይ የነበረው ድርድር ወደ ውሃ ድርሻ ድርድር ዞሯል” ያሉት ኃላፊው በግድቡ ጉዳይ ብዙውን ጊዜ ከኢትዮጵያ ጐን ትሠለፍ የነበረችው ሱዳንም ከግብጽ ጋር ወግናለች ብለዋል፡፡
ድርድሩ እየተካሄድ ያለው ኢትዮጵያ በአሜሪካ፣ አለም ባንክ፣ ሱዳን እና ግብጽ ጫና ስር ወድቃ 4 ለ1 በሆነ ሁኔታ ነው ሲሉ ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡
በአሜሪካ ሲካሄድ በቆየው ድርድር ጉዳዩ ለመገናኛ ብዙሃን ቀደም ባለው ሣምንት ማብራሪያ የሰጡት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ድርድሩ ከተቋጨ በኋላ ለፊርማ የተዘጋጀው ሰነድ የተሟላ ሆኖ ባለመገኘቱ በኢትዮጵያ በኩል ውድቅ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
ድርድሩ የውሃ ድርሻ ክፍፍል መልክ እንደነበረው ያረጋገጡት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ በኩል ተገቢ ያልሆነ ስምምነት እንዳይፈርም ጥንቃቄ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በበኩላቸው ቀደም ባለው ሣምንት ፓርላማው ባቀረቡት ማብራሪያ ስምምነቱ እንዲዘገይ ማድረጋቸውን አስገንዝበዋል፡፡  


Read 1484 times
Administrator

Latest from Administrator