Thursday, 20 February 2020 00:00

ከማልታ የትራፊክ ፖሊሶች 75 በመቶው በሙስና ታሰሩ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የማልታ መንግስት የአገሪቱን የትራፊክ ፖሊስ ዋና አዛዥ ጨምሮ 75 በመቶ ያህል የትራፊክ ፖሊሶችን በሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር ማዋሉን ዘ ኢንዲፔንደንት ከትናንት በስቲያ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
በትንሽዋ የሜዲትራንያን ባህር ደሴት ማልታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙት 50 የትራፊክ ፖሊሶች መካከል 37ቱ ያልሰሩበትን የትርፍ ጊዜ ክፍያና ውሎ አበል መውሰድ፣ ነዳጅ ማጭበርበርና ከአሽከርካሪዎች ጉቦ መቀበልን ጨምሮ የተለያዩ የሙስና ወንጀሎችን መፈጸማቸው መረጋገጡን ተከትሎ፣ ባለፈው ማክሰኞ መታሰራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት አቤላ፣ ሙስናን ለማጥፋት የሚደረገው መሰል እርምጃ ወደ ሌሎች የመንግስት ሰራተኞች እንደሚቀጥል መናገራቸውንም አመልክቷል፡፡
በቁጥጥር ስር የዋሉት የትራፊክ ፖሊሶች፣ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፤ የአገሪቱ ዋና ፖሊስ አዛዥ ከወራት በፊት በአገሪቱ የተፈጸመን ሙስና በምርመራ በማጋለጧ ለእስር ከተዳረገች አንዲት ጋዜጠኛ ግድያ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውንም አስታውሷል፡፡

Read 5561 times