Saturday, 22 February 2020 12:18

በቻይና የሞባይል ሽያጭ በ50 በመቶ እንደሚቀንስ ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መስፋፋት ጋር በተያያዘ በቻይና የሩብ አመቱ የሞባይል ምርት በ50 በመቶ ያህል ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፤ በአለማቀፉ የሞባይል ስልኮች ገበያ ላይ መቀዛቀዝ እንደሚከሰትና በ5 አመት ውስጥ ዝቅተኛው የሩብ አመት የሞባይል ሽያጭ ይመዘገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በቻይናም ሆነ በሌሎች አገራት የሚገኙ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባንያዎች ከቫይረሱ ስርጭት ጋር በተያያዘ ስራቸው መስተጓጎሉንና የሰው ሃይል እጥረት ማጋጠሙን ተከትሎ፣ የሩብ አመቱ የሞባይል ምርት መጠን በ12 በመቶ ያህል ሊቀንስ እንደሚችል መነገሩን ዘገባው አመልክቷል፡፡
በሩብ አመቱ የሞባይል ሽያጩ በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቀው ኩባንያ አፕል ሲሆን ኩባንያው የሚያመርተው አይፎን ሞባይል፤ የሩብ አመት ሽያጭ በ10 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል፡፡
ተፎካካሪው የደቡብ ኮርያው ሞባይል አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ በበኩሉ፤ የሽያጭ መጠኑ በ3 በመቶ ያህል ሊቀንስበት እንደሚችልም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 1614 times