ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መስፋፋት ጋር በተያያዘ በቻይና የሩብ አመቱ የሞባይል ምርት በ50 በመቶ ያህል ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፤ በአለማቀፉ የሞባይል ስልኮች ገበያ ላይ መቀዛቀዝ እንደሚከሰትና በ5 አመት ውስጥ ዝቅተኛው የሩብ አመት የሞባይል ሽያጭ ይመዘገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በቻይናም ሆነ በሌሎች አገራት የሚገኙ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባንያዎች ከቫይረሱ ስርጭት ጋር በተያያዘ ስራቸው መስተጓጎሉንና የሰው ሃይል እጥረት ማጋጠሙን ተከትሎ፣ የሩብ አመቱ የሞባይል ምርት መጠን በ12 በመቶ ያህል ሊቀንስ እንደሚችል መነገሩን ዘገባው አመልክቷል፡፡
በሩብ አመቱ የሞባይል ሽያጩ በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቀው ኩባንያ አፕል ሲሆን ኩባንያው የሚያመርተው አይፎን ሞባይል፤ የሩብ አመት ሽያጭ በ10 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል፡፡
ተፎካካሪው የደቡብ ኮርያው ሞባይል አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ በበኩሉ፤ የሽያጭ መጠኑ በ3 በመቶ ያህል ሊቀንስበት እንደሚችልም ዘገባው አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል