Print this page
Saturday, 22 February 2020 12:27

የናሚቢያ ቀዳማዊት እመቤት ሙሉ ሃብታቸውን ለበጎ አድራጎት እንደሚሰጡ አስታወቁ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

            ጄፍ ቤዞስ 10 በመቶ ሃብታቸውን ለአየር ንብረት ለውጥ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል

         የናሚቢያ ቀዳማዊት እመቤት ሞኒካ ጄኒጎስ ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ 3 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ሃብታቸው በሙሉ ለበጎ አድራጎት እንዲውል መወሰናቸውን እንዲሁም የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ ከአጠቃላይ ሃብታቸው 10 በመቶ ያህሉን ወይም 10 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባር እንደሚለግሱ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡
በአገራቸው የጾታ ልዩነትን ማጥፋትን ጨምሮ የተለያዩ የበጎ ምግባር ስራዎችን በመስራት የአፍሪካውያን ቀዳማዊ እመቤቶችን ገጽታ ለመገንባት እየጣሩ የሚገኙት ሞኒካ ጄኒጎስ፤ሃብታቸውን ለበጎ ምግባር ለማዋል መወሰናቸውን እንዳስታወቁ ዘገባው አመልክቷል፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ አሜሪካዊው የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ፤ ከአጠቃላይ ሃብታቸው 10 በመቶ ያህሉን ወይም 10 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባር እንደሚለግሱ ባለፈው ሰኞ ማስታወቃቸው ተነግሯል፡፡
የአማዞኑ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጄፍ ቤዞስ አዲስ ባቋቋሙት ቤዞስ አርዝ ፈንድ የተባለ ፋውንዴሽን አማካይነት በአለማቀፍ ዙሪያ ለሚደረጉ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዙ እንቅስቃሴዎች የ10 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደሚያደርጉ ነው የተናገሩት፡፡ የገንዘብ ድጋፉ ከሚደረግላቸው መካከል በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚሰሩ ተመራማሪዎች፣ አክቲቪስቶች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚገኙበት የዘገበው ፎርብስ መጽሄት፣ ተፈጥሮን በመንከባከብ ላይ ትኩረት ላደረጉ ቅድሚያ ይሰጣል መባሉንም ገልጧል፡፡ የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆኑት ጄፍ ቤዞስ አጠቃላይ የተጣራ ሃብታቸው 129.9 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡

Read 4217 times
Administrator

Latest from Administrator