Saturday, 21 March 2020 12:57

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለጤና ሚኒስቴር የ10 ሚ.ብር ድጋፍ አደረገ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    ሁኔታዎችን እያየን ድጋፉን እንቀጥላለን›› - አቶ አቤ ሳኖ የባንኩ ስራ አስኪያጅ

            የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለውንና የአለም ስጋት የሆነውን ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19)ን ቀድሞ ለመከላከል የሚረዳ የ10.ሚ ብር ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር ሰጠ፡፡ ባንኩ ትላንት በዋና መሥሪያ ቤቱ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታዋና የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ነው ድጋፉን ያስረከበው፡፡
የባንኩ ስራ አስኪያጅ አቶ አቤ ሳኖ ድጋፉን ለጤና ሚኒስትር ዴኤታ ካስረከቡ በኋላ ባደረጉት ንግግር ባንኩ ኮሮና ቫይረስ መከሰቱን ተከትሎ ስርጭቱን ለመቆጣጠር ያደረገው የመጀመሪያ ድጋፍ መሆኑን ገልፀው ሁኔታው እየታየ ድጋፉ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታዋ በበኩላቸው ችግሩን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ፈጣን ምላሽ የሰጠውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አመስግነው ይህን ውሳኔ በፍጥነት የወሰኑትን የባንኩን አመራሮች አመስግነዋል፡፡ የባንኩን አርአያ በመከተል ሌሎችም የመንግሥትና የግል ተቋማት ለዚህ አገራዊ ጥሪ ምላሽ እንዲሰጡና ችግሩን ለመቅረፍ የሚደረገውን ትግል እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Read 2785 times