Saturday, 28 March 2020 11:30

የቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ መልዕክት - ለኢትዮጵያ ህዝብ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

      የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በጥሬ ገንዘብ ብር 3,500,000 (ሦስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ ብር ለገሰ

            በአለም ላይ የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ በቂ ክትትልና ትኩረት ተሰጥቶት አስቸኳይ እርምጃ ካልተወሰደ የሚያመጣው ጥፋት እጅግ አሰቃቂ መሆኑን ተቋማችን ከመጀመሪያው ጊዜ አንስቶ ግንዛቤ ወስዷል፡፡ ይህንኑ ሁኔታ ለመቋቋም መጀመሪያ ራስንና አካባቢን የግንዛቤ ትምህርት በመስጠት መንቀሳቀስ እንደሚኖርብን በማመን፣ የስራ መርሀ ግብር በመንደፍና በየፋብሪካዎቻችን አንድ አንድ ግብረ ሃይል በማቋቋም፣ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመርን ውሎ አድሯል፡፡
በዚሁ መሰረት ፋብሪካዎቻችን በሚገኙበት በአዲስ አበባ፣ በኮምቦልቻ፣ በሃዋሳ፣ በማይጨው፣ በጉብሬ ወልቂጤና ዝዋይ የራሳችንን ሰራተኞችና የአካባቢውን ህብረተሰብ በመጨመር ፤ ችግሩን በጥልቀት እንዲረዱና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል፤በየፋብሪካዎቻችን በሁሉም መግቢያ በሮች ላይ ሰራተኞቻችንም ሆነ እንግዶች በሙቀት መቆጣጠሪያ እየተለኩና በስነ-ስርዐት እንዲታጠቡ በማድረግ እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፤በቂ ርቀት በአቀማመጥ ወቅት እንዲኖር ለማስቻል የሰራተኞች ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እንዲጨምር ተደርጓል፤በየፋብሪካው እንግዳውና ሰራተኞች የሚስተናገዱበት የሰራተኞች ክበብ ለጥንቃቄ ሲባል ተዘግቷል፤
ፋብሪካዎቻችን በሚገኙበት አካባቢ፣ ከህብረተሰቡና ከአካባቢው የስራ ሀላፊዎች ጋር በመሆን፣ የገንዘብና የቁሳቁስ እርዳታዎች አድርገናል፤
በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚከናወኑ ስራዎች ደግሞ ለጤና ሚኒስቴር
በጥሬ ገንዘብ ብር 3,500,000 (ሦስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ) ከመለገስም አልፎ በየከተሞች የሚገኙትን የማስታወቂያ ግዙፍ ሰሌዳዎቻችንን፣ የጤና ሚኒስቴር የሚያወጣቸውን መልእክቶች እንዲያስተላልፍበት  ፈቅደናል፡፡
እንዲሁም በስራ አጋሮቻችን ለስራ የምንጠቀምባቸው ከፍተኛና መለስተኛ የጭነት መኪናዎች በተፈለጉበት ጊዜ ሁሉ ለማቅረብ ዝግጁ ነን፡፡
ምንግዜም ቢሆን ችግርን አሸንፈን የመወጣት ባህላችንን ዛሬም እንደምንደግመው ቢ.ጂ.ኣይ ኢትዮጵያ ፍጹም እምነቱ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ ጤንነትን
እየተመኘ፣ ይሄንን ችግር በጋራ በአጭር ጊዜ እንደምንወጣው ተስፋ በማድረግ ጭምር ነው፡፡
ቢ.ጂ.ኣይ ኢትዮጵያ

Read 12035 times Last modified on Saturday, 28 March 2020 15:44