Monday, 08 June 2020 00:00

የፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዝምታን በመምረጥ ነውረኛን አናጎብዝ!
የተቀመጡበት የመሪነት ወንበር እርቃንን በአደባባይ የመቆም ያህል ለትችት አጋልጦ ይሰጣልና ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እሚያራምዱት ፖሊሲ ላይም ይሁን እሚወስኑት ውሳኔ ላይ የሚነሱ ትችቶችን እንደ ጠቃሚ ግብአት መውሰድ ተገቢ ነው፡፡ እኛን ጨምሮ ከፊት ያስቀደሙት አንድ መቶ አስር ሚሊየን ህዝብ በሰጡትና ባልሰጡት ልክ ያመሰግናቸዋል፤ ይወቅሳቸዋል፡፡ ይህ እሳቸው መሪ፣ እኛ ህዝብ መሆናችን የሰጠን የመሪና ተመሪነት ኮንትራት ነው፡፡
ከዚህ ቀደም ጀዋር አህመድ የመናዊ ነው የሚል ሀሳብ ከምናከብራቸው አንድ ተጽእኖ ፈጣሪ ሰው ሰምተን …. እንዳልሰማን በማለፋችን፣ ነውርን እያየን በዝምታ አልፈናል፤ እኛንም ከነውረኛ አስቆጥሮናል፡፡ ሰሞኑን የዝምታችን ጥልቀት ያጎበዛቸው ሌላ ተናጋሪ፣ በቲ ኤም ኤች ብቅ ብለው ጀዋር ላይ ሲደረግ ዝም ያልነውን ነውር በድጋሚ አለማምደውናል፡፡ ጠቅላያችን ኢትዮጵያዊ እንዳልሆኑ ፈረንጆች እንደነገሯቸው በእርግጠኝነት ተናግረዋል፡፡
ሀሳብን በነጻነት መግለጽ ሰው ከመሆን የሚወለድ መብት ስለሆነ እከሌ ሰጠኝ ብለን አናመሰግን ይሆናል …. ይህ መብት የሚያረጋግጠው የዘለፋ አንቀጽ እንደሌለ ግን እርግጠኛ ነን …. እንደውም ከችሮታው ጋር የሚያያዝ የሌላውን መብት የማክበር ግዴታን ያጸናል፡፡ የጠቅላያችን ደም ከኢትዮጵያ መሆንና አለመሆኑ ብቻውን ፤ የጠቅላያችን ብሔር ከዚህ ወይም ከዚያኛው ብሔር መሆኑ በራሱ … የመሪነት አቅማቸው ላይ ከነጠላ ጸጉር ያነሰ አስተዋጥኦ እንደማይኖረው እናውቃለን፡፡
ይህንን ጽሁፍ የምንጽፈው በሆነ ተአምር እሳቸው አይን ላይ ደርሶና አንብበውት እንዲጽናኑ አይደለም …. ይልቁንም ይሄ ጊዜ አልፎ ነገ ልጆቻችንና የልጅ ልጆቻችን፣ ”ያኔ እንዲህ አይነት ነውር ሲነገር አንተ ወይም አንቺ ምን ብላችሁ ነበር” ቢሉን የምንመልሰው እንዳናጣ ነው፡፡ እያየንና እየሰማን ዝም በማለት ነውረኛን አናጎብዝ !!!
(መላ ቲዩብ)
***

Read 1044 times