Print this page
Monday, 24 August 2020 18:08

የአመቱ 500 ግዙፍ የአለማችን ኩባንያዎች ይፋ ተደረጉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ዎልማርት በ523.9 ቢ ዶላር ገቢ፣ አምራኮ ደግሞ በ329.7 ቢ ዶ ላር ትርፍ ቀዳሚነቱን ይዘዋል

               ከአለማችን ኩባንያዎች መካከል በየአመቱ ከፍተኛ ገቢና ትርፍ ያስመዘገቡትን 500 ግዙፍ ኩባንያዎች ዝርዝር ይፋ የሚያደርገው ፎርቹን መጽሔት፤ ከሰሞኑም የ2019 የአለማችን ግዙፍ ኩባንያዎችን ዝርዝር ያወጣ ሲሆን የአሜሪካው ዎልማርት በ523.9 ቢሊዮን ዶላር ገቢ፣ የሳኡዲው የነዳጅ ኩባንያ አምራኮ ደግሞ በ329.7 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ የአንደኛነት ደረጃን ይዘዋል፡፡
ሲኖፔክ ግሩፕ 407 ቢሊዮን ዶላር፣ ስቴት ግሪድ 383.9 ቢሊዮን ዶላር፣ ቻይና ናሽናል ፔትሮሊየም 379.1 ቢሊዮን ዶላር፣ ሮያል ደች ሼል 352.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት እንደ ቅደም ተከተላቸው ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን ኩባንያዎች መሆናቸውንም ፎርቹን አስታውቋል፡፡
ከሳኡዲው አምራኮ በመቀጠል በአመቱ ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ከፍተኛ ትርፍ ያስመዘገቡ የአለማችን ኩባንያዎች ደግሞ፣ 254.6 ቢሊዮን ዶላር ያተረፈው ቤክሻየር ሃታዌይ፣ 260.1 ቢሊዮን ዶላር ያተረፈው አፕል፣ 177 ቢሊዮን ዶላር ያተረፈው ኢንዱስትሪያል ኤንድ ኮመርሺያል ባንክ ኦፍ ቻይና እና 125.8 ቢሊዮን ዶላር ያተረፈው ማይክሮሶፍት ኩባንያ ናቸው፡፡
ከ32 አገራት ተመርጠው የተካተቱት የአመቱ የአለማችን 500 ግዙፍ ኩባንያዎች በፈረንጆች አመት 2019 በድምሩ 33.3 ትሪሊዮን ዶላር ገቢ እና 2.1 ትሪሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘታቸውን እንዲሁም ከ69.9 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም መጽሔቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 4748 times
Administrator

Latest from Administrator