የፌስቡኩን መስራች ማርክ ዙከርበርግና የማይክሮሶፍቱን መስራች ቢል ጌትስን ጨምሮ 9 አሜሪካውያን ቢሊየነሮች ባለፈው ሰኞ ብቻ በድምሩ 14 ቢሊዮን ዶላር ያህል ኪሳራ እንዳጋጠማቸው ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘግቧል፡፡
በዕለቱ በአሜሪካ የተለያዩ የአክሲዮን ገበያዎች የዋጋ ቅናሽ መከሰቱን ተከትሎ፣ ቢሊየነሮቹ በድምሩ 14 ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ማርክ ዙከርበርግ ከፍተኛውን የ2.8 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠመው አመልክቷል፡፡
ቢል ጌትስ ሰኞ ዕለት ሃብቱ በ1.7 ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 115 ቢሊዮን ዶላር ያህል መድረሱን የገለጸው ዘገባው፤ ከአስሩ የአሜሪካ ዋነኛ ባለጸጎች መካከል በዕለቱ የሃብት መጠኑ የጨመረው የአማዞኑ መስራች ጄፍ ቤዞስ ብቻ መሆኑንም አመልክቷል፡፡
Tuesday, 03 November 2020 00:00
ዘጠኝ የአሜሪካ ቢሊየነሮች በ1 ቀን ብቻ 14 ቢሊዮን ዶላር ከስረዋል
Written by Administrator
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል