Print this page
Thursday, 19 November 2020 00:00

ሳምሰንግ በሞባይል ሽያጭ 1ኛ ደረጃን ይዟል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአለማቀፉ የስማርት ፎን ሞባይል ስልኮች ገበያ ያለፈው ሩብ አመት ሽያጭ ሳምሰንግ 80.2 ሚሊዮን ምርቶችን በመሸጥና 23 በመቶ የገበያ ድርሻ በመያዝ ቀዳሚ መሆኑን ቴክኒውስ ዘግቧል፡፡
የቻይናው ሁዋዌ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 51.7 ሚሊዮን የሞባይል ስልክ ምርቶችን በመሸጥና በአለማቀፉ የሞባይል ገበያ የ14.9 በመቶ ድርሻ በመያዝ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፤ ሌላኛው የቻይና ኩባንያ ዚያኦሚ በበኩሉ 47.1 ሚሊዮን ስልኮችን በመሸጥ በ13.5 በመቶ ድርሻ ሶስተኛ ደረጃን መያዙን አመልክቷል።
በሩብ አመቱ በከፍተኛ መጠን በመሸጥ ቀዳሚነቱን የያዙት የሞባይል አይነቶች የአፕል ኩባንያ ምርት የሆኑት አይፎን 11 እና አይፎን ኤስኢ 2020 መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ እንደ ቅደም ተከተላቸው በብዛት በመሸጥ ከሶስተኛ እስከ አምስተኛ ደረጃን የያዙት ደግሞ የሳምሰንግ ምርት የሆኑት ጋላክሲ ኤ21ኤስ፣ ጋላክሲ ኤ11 እና ጋላክሲ ኤ51 መሆናቸውንም ገልጧል፡፡

Read 4900 times
Administrator

Latest from Administrator