Tuesday, 01 December 2020 00:00

ትራምፕ በ15 የአፍሪካ አገራት ላይ አዲስ የጉዞ ገደብ ጥለዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ተሰናባቹ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ15 የአፍሪካ አገራት መንገደኞች ላይ አዲስ የጉዞ ገደብ የጣሉ ሲሆን፣ የአገራቱ መንገደኞች ከቀጣዩ ወር ጀምሮ ወደ አሜሪካ መግባት የሚችሉት አስቀድመው እስከ 15 ሺህ ዶላር በቦንድ መልኩ ካስያዙ ብቻ ነው መባሉ ተዘግቧል፡፡ የትራምፕ አስተዳደር ጊዜያዊ ያለውን የጉዞ ገደብ የጣለባቸው አገራት አንጎላ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ቻድ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ጅቡቲ፣ ኤርትራ፣ ጋምቢያ፣ ጊኒቢሳኡ፣ ላይቤሪያ፣ ሊቢያ፣ ሞሪታኒያ፣ ሱዳን፣ ሳኦ ቶሜና ፕሪንሲፔ፣ ኬፕ ቨርዴ እና ብሩንዲ እንደሆኑ የዘገበው ቢቢሲ፤ በአገራቱ ላይ አዲሱን ገደብ መጣል ያስፈለገው ወደ አሜሪካ ከገቡ የአገራቱ መንገደኞች መካከል ከ10 በመቶ በላይ የሚሆኑት ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ እንደሚቆዩ በመረጋገጡ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
የአገራቱ መንገደኞች በቦንድ የሚያስይዙት ገንዘብ ከአሜሪካ ሲወጡ እንደሚመለስላቸው የጠቆመው ዘገባው፤ አዲሱ የጉዞ ገደብ ለ6 ወራት ያህል ተሞክሮ ውጤታማ መሆኑ ከተረጋገጠ ቀጣይ እንዲሆን ይደረጋል መባሉንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 3159 times