Print this page
Saturday, 05 December 2020 19:17

“የሀገሬ ጥያቄ” የኪነ-ጥበብ ምሽት ረቡዕ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት የሚያዘጋጀው ወርሃዊ የኪነ-ጥበብ ምሽት የዚህ ወር መሰናዶ “የሀገሬ ጥያቄ” በሚል ርዕስ የፊታችን ረቡዕ ህዳር 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ጊዮን ሆቴል ውስጥ በሚገኘው ግሮቭ ጋርደን ዎክ ውስጥ ይካሄዳል።
ይህ ምሽት በኮቪድ 19 የምሽት መቋረጦች በኋላ የሚካሄድ የሰምና ወርቅ የመጀመሪያው መሰናዶ እንደሚሆን የመርሃ ግብሩ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ ተናግሯል።
በዕለቱ ወዳጄነህ ማህረነ (ዶ/ር)፣ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፣ አንጋፋዋ ከያኒ አለምፀሐይ ወዳጆ ፣ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ ረ/ፕ ነብዩ ባዬ፣ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም፣ አርቲስት ሱራፌል ተካ፣ ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰው፣ ጋዜጠኛ ሰለሞን ሀይለየሱስ፣ ገጣሚ ገዛኸኝ ጤራ እና ገጣሚ መንበረማርያም ሀይሉ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል። የመግቢያ ዋጋው 100 ብር ሲሆን ትኬቶቹ በብሄራዊ ቴአትር የሰምና ወርቅ የመፅሐፍት አውደ ርዕይ ላይ እንደሚገኙም ታውቋል።

Read 14400 times
Administrator

Latest from Administrator