Print this page
Saturday, 05 December 2020 19:17

አገር አቀፍ የቁንጅና ውድድር ነገ በእንጦጦ ፓርክ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ኢስት አፍሪካ ኢንተርቴይመንትና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ከፌደሬሽን ምክር ቤት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና 10ሩ ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተሳተፉበት ቁንጅና ውድድር ነገ  ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በሸገር ፓርክ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
የቁንጅና ውድድሩን ክልላቸውን በመወከል ከአንድ እስከ ሶስተኛ በመውጣት የሚያሸንፉ የሰላምና የአንድነት አምባሳደር ሆነው ክልሎቻቸውን እንደሚገለግሉ የኢስት አፍሪካ ኢንተርቴይመንትና ኢቨንት ኦርጋናይዘር መስራችና ዋና ስራ አስኪጅ አቶ ሞቲ ሞረዳ ባለፈው ረቡዕ ረፋድ ላይ በሀያት ሬጀንዲ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀው ነገ በሚካሄደው ውድድር ላይ ሁለተኛና ሶስተኛ የሚወጡ ቆነጃጅት ሽልማትና አምባሳደርነታቸውን ከክብር እንግዶች እንደሚቀበሉም   ተናግረዋል።
ከየክልሉ 1ኛ የሚወጡ አሸናፊዎች ደግሞ 15ኛው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል ዕለት ከኢፌደሪ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴና ከጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) እጅ እንደሚቀበሉም ታውቋል።
የቁንጅና ውድድሩ ዋና አላማ አሁን አገራችን ያለችበትን በዘርና በሃይማኖት ተከፋፍሎ መባላትና መናቆር ያስከተለውን ችግር ለመቅረፍ ቆነጃጅቱ ለየክክላቸው ወጣቶች አንድነት፣ ፍቅርና ሰላም ላይ አበክረው እንደሚሰሩና በቀጣዩ አመት ለቀጣዮቹ አምባሰደሮች ሃላፊነታቸውን እስከሚያስረክቡ ድረስ ይሰራሉም ተብሏል።


Read 14561 times
Administrator

Latest from Administrator