Monday, 07 December 2020 00:00

አዲሱ የኦባማ መጽሐፍ በሽያጭ ክብረወሰን አስመዘገበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በቅርቡ ለንባብ ያበቁት “ኤ ፕሮሚስድ ላንድ” የተሰኘው መጽሐፍ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በ1.7 ሚሊዮን ቅጂዎች መሸጡንና በዚህም አዲስ የሽያጭ ክብረወሰን ማስመዝገብ መቻሉን ዴይሊ ሜይል ዘግቧል፡፡
መጽሐፉ በአሜሪካና ካናዳ ታትሞ ለገበያ በቀረበበት የመጀመሪያው ቀን ብቻ ከ887 ሺህ በላይ ቅጂዎች እንደተሸጡ ያስታወሰው ዘገባው፣ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በ1 ሚሊዮን 710 ሺህ 443 ቅጂዎች በመሸጥ አዲስ ክብረ ወሰን ማስመዝገቡን ፔንጉዊን ራንደም ሃውስ የተባለው የመጽሐፉ አሳታሚ ድርጅት ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ሽያጩ የወረቀት፣ የድምጽና የዲጂታል ቅጂዎችን እንደሚያጠቃልል የጠቆመው ዘገባው፣ በመጀመሪያ ዙር በ3.4 ሚሊዮን ቅጂዎች የታተመው “ኤ ፕሮሚስድ ላንድ” ከሰሞኑ በተጨማሪ ቅጂዎች እንደታተመና እስካሁን ድረስ ለህትመት የበቃው አጠቃላይ ቅጂ 4.3 ሚሊዮን መድረሱንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2988 times