የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በቅርቡ ለንባብ ያበቁት “ኤ ፕሮሚስድ ላንድ” የተሰኘው መጽሐፍ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በ1.7 ሚሊዮን ቅጂዎች መሸጡንና በዚህም አዲስ የሽያጭ ክብረወሰን ማስመዝገብ መቻሉን ዴይሊ ሜይል ዘግቧል፡፡
መጽሐፉ በአሜሪካና ካናዳ ታትሞ ለገበያ በቀረበበት የመጀመሪያው ቀን ብቻ ከ887 ሺህ በላይ ቅጂዎች እንደተሸጡ ያስታወሰው ዘገባው፣ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በ1 ሚሊዮን 710 ሺህ 443 ቅጂዎች በመሸጥ አዲስ ክብረ ወሰን ማስመዝገቡን ፔንጉዊን ራንደም ሃውስ የተባለው የመጽሐፉ አሳታሚ ድርጅት ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ሽያጩ የወረቀት፣ የድምጽና የዲጂታል ቅጂዎችን እንደሚያጠቃልል የጠቆመው ዘገባው፣ በመጀመሪያ ዙር በ3.4 ሚሊዮን ቅጂዎች የታተመው “ኤ ፕሮሚስድ ላንድ” ከሰሞኑ በተጨማሪ ቅጂዎች እንደታተመና እስካሁን ድረስ ለህትመት የበቃው አጠቃላይ ቅጂ 4.3 ሚሊዮን መድረሱንም አክሎ ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል