Tuesday, 08 December 2020 00:00

በየ100 ሰከንዱ 1 ህጻን በኤችአይቪ እንደሚጠቃ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአለም ዙሪያ በየ100 ሰከንዱ 1 ህጻን በኤችአይቪ ቫይረስ እንደሚጠቃ እና ባለፈው የፈረንጆች አመት 2019 በመላው አለም 110 ሺህ ያህል ህጻናት በኤድስ ምክንያት ለሞት መዳረጋቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ከሰሞኑ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡
በአመቱ በመላው አለም 320 ሺህ ያህል ህጻናትና ወጣቶች በቫይረሱ መያዛቸውን ያስታወቀው ድርጅቱ፤ በቫይረሱ የሚያዙና ለሞት የሚዳረጉ ህጻናት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ሲሆን የጸረ ኤች አይቪ ህክምና አገልግሎት በበቂ ሁኔታ እያገኙ እንዳልሆነም ገልጧል፡፡
ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ለህጻናት፣ ወጣቶችና ነፍሰጡር እናቶች የሚሰጡ የጸረ ኤች አይቪ ህክምና አገልግሎቶች በከፍተኛ ሁኔታ እየተስተጓጎሉ እንደሆነ የጠቆመው የድርጅቱ ሪፖርት፤ መንግስታት አገልግሎቶቹን ለማሟላት ከፍተኛ ጥረት ማድረግ እንደሚገባቸውም አመልክቷል፡፡
በ2019 የፈረንጆች አመት በመላው አለም 1.7 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በኤችአይቪ ቫይረስ መጠቃታቸውን ያስታወሰው የተመድ የዜና ድረገጽ በበኩሉ፣ በአመቱ በድምሩ 690 ሺህ ያህል ሰዎች ከኤችአይቪ ጋር በተያያዘ ለሞት መዳረጋቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2727 times