Saturday, 19 December 2020 09:49

ተፈላጊዎቹን “የህወሃት ጁንታ” አመራሮች ለጠቆመ 10 ሚሊዮን ብር!

Written by 
Rate this item
(4 votes)

 የአቦይ ስብሃት ልጅ መገደሉ ተረጋገጠ
                               
             ተፈላጊዎቹ “የህወኃት ጁንታ” አመራሮች ያሉበትን ለጠቆመ 10 ሚሊዮን ብር የማበረታቻ ሽልማት እንደሚሰጥ የመከላከያ ሰራዊት  ትላንት አስታውቋል፡፡
10 ሚሊዮን ብሩ መንግስት የወሰደውን ህግ የማስከበር እርምጃ በመሸሽ የተደበቁትን የህወኃት አመራሮች ያሉበትን ቦታ ለሚያውቅና ለሚጠቁም እንዲሁም ተፈላጊዎቹን አሳልፎ ለሚሰጥ አካል የሚበረከት መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት የህብረተሰብ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ተናግረዋል፡፡ የህወኃት አመራሮች ጦር በማስተማር ሲመራ የነበረው የአቦይ ስበሃት ልጅ ተከስተ ስብሃት ነጋ በገበሬው መገደሉ መረጋገጡ ተገልጿል። ከሚፈለጉት የህወኃት ከፍተኛ አመራሮችም መካከል የተያዙም የተገደሉም እንደሚገኙ የጠቆሙት  ጀነራል ባጫ ደበሌ  ሁሉን ነገር ከተጣራና ከተመረመረ በኋላ ይፋ ይደረጋል ብለዋል፡፡

Read 12405 times