Print this page
Saturday, 02 January 2021 14:07

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

 ምፀት

የዘንድሮው እግዜር የኦሪቱ አይደለም፣
ጥፋት ስታጠፋ- ከገነት አውጥቶ
አያባርርህም፤
የዘንድሮ እግዜር-ኃጢአንን ሲቆጣ፤
ፓርላማ ይሰዳል-ህሊናውን ትቶ እጁን
እንዲያወጣ
እየጠበኳት ነው
እየጠበኳት ነው- በሰው ሁሉ መሃል
እንደይረጋግጧት ብዬ- የኔን ውብ
ሀመልማል፤
እየጠበኳት ነው -እንዳትጠፋ ድንገት
መና ሆና እንድትኖር-ሳለ እርጅና ሞት፤
እየጠበኳት ነው - እንዳትጠፋ ጭራሽ
የኔን ገጸ ጸዳይ፤ የሕመሜን ፈዋሽ
እየጠበኳት ነው-ከሰው ከአራዊቱ፣
እስከ ነፃነት ቀን- እስኪነጋ ሌቱ፡፡
(“ነፃነት” ግጥሞችና ወጎች፤ ወሰንሰገድ ገብረ ኪዳን)

Read 2828 times
Administrator

Latest from Administrator