በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ስዕሎች ለእይታ የሚቀርቡበት “ግድቡ የኔ ነው” የተሰኘ የስዕል ዐውደ ርዕይ ዛሬ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል ይከፈታል። 6 ሰዓሊያን ከህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት፣ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ አውደ ርዕይ ላይ ሰአሊያኑ ብሩክ የሺጥላ ፣ብርሃን በየነ፣ ሜሮን ኤርሚያስ፣ እስራኤል ወ/ገብርኤል፣ ኤፍሬም ተፈራና ሰለሞን ግዛው ስእሎቹ በሙሉ የህዳሴው ግድብ ላይ ትኩረት እድርገው የተሰሩ ሲሆን ፣እያንዳንዱ ሰዓሊ 5 ስራዎችን እንደሚያቀርብና በአጠቃላይ 30 ስዕሎች ለእይታ እንደሚበቁ ሰዓሊ ብርሀን በየነ ገልፃለች፡፡
አውደ ርዕዩ እስከ ሰኞ ጥር 17 አመሻሽ ድረስ ለእይታ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
Saturday, 23 January 2021 14:42
“ግድቡ የኔ ነው” የስዕል አውደ ርዕይ ዛሬ ይከፈታል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና