Print this page
Saturday, 30 January 2021 16:32

ትኩረት የሚሻው የንፅህና አገልግሎት አቅርቦት

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  ዋናው ነገር ጤና፡፡ እውነት ነው፡፡ የጤና መሰረተ ደግሞ ንፅሀና ነው፡፡ ንፅህናናንን ለመጠበቅ የንፁህ ውሀ እና መፀዳጃ ቤት አቅርቦት ወሳኝነት አለው፡፡ እንደ ዩኒሴፍ መረጃ ከ60-80 በመቶ የሚሆነው ተላላፊ በሽታ የሚከሰተው በንፅህና አገልግሎት እና ውሀ አቅርቦት እጥረት ይከሰታል፡፡ የንፅህና አገልግሎት  ገጠርም ከተማ የማይል በሁሉም ቦታ ሊስፋፋ የሚገባ መሰረታዊ ነገር ነው ፡፡ እንደ ዓለም ዓቀፍ የጤና ድርጅት መረጃ መሰረት ከ600 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የከተማ ነዋሪዎቸ ለበቂ የንፅህና አገልግሎት ተደራሽ አይደሉም፡፡ በኢትዮጵያ የከተማ ነዋሪ ቁጥር እየጨመረ ሲሆን በዓለም ባንክ የ2019 መረጃ መሰረት በአማከይ 2.6 በመቶ ይጨምራል፡፡ በገጠር ደህም 80 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ይኖራል፡፡ የምዕተ ዓመቱን ግብ አሁን ደግም ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት፣ ችግሮች እንዳሉ ሆነው እጅ የመታጠብ ባህልን ለማስረፅ፣ ሜዳ ላይ መፀዳዳጽን ለማስቀረት እና ሽንት ቤት በየሁሉም ቤት ለማዳረስ ብዙ ጥረት ተደርጓል፡፡
በጥቅሉ ሲታይ በምዕት ዓመቱ የልማት ግብ ዙርያ በተለይ በውሀ እርቦት ዙርያ ጉልህ ውጤት የተመዘገበ ቢሆንም፣ በንፅህና(ሳኒቴሽ) ረገድ የታለመውን ማሳካት ባይችልም የተወሰኑ ለውጦች ታይተዋል፡፡ ይህንን ለመቅረፍ እ.ኤ.አ እስከ 2030 የሚቆዩ ዘላቂ የልማት ግቦች የምዕምተ ዓመቱን የልማት ግባች ተክተው እየተተገበሩ ይገኛሉ፡፡ በዚህም መሰረት ዘላቂ የልማት ግብ ቁጥር 6 “ለሁሉም ተደራሽ የሆነ የውሀ እና ሳኒቴሽን አቅርቦትን ማረጋገጥ” የሚል ዓላማ አለው፡፡ ይህ አላማ ሶስት አንኳር ጉዳዮችን ይመለከታል፡፡ እነዚህም የመጠጥ ውሀ አቅርቦት፣ ንፅህናና እና ቆሻሻ ውሀ አወጋገድ ናቸው፡፡ ይህንን ግብ ለማሳካት ኢትዮጵያም በተቀናጀ መልኩ በዘርፉ ያሉ መስሪያ ቤቶችን እና የልማት አጋሮችን በማካተት በገጠር፣ በከተማ እና በተቋማት የንፅህና እና ውሀ አቅርቦት ለማሻሻል እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡
ስለንፅህና አገልግሎት አቅርቦት እና አስፈላጊነት ግንዛቤ ለመፍጠር እና የጉዳዩን አስፈላጊነት ለማጉላት በዓለም ዓቀፍ እና ሀገር ዓቀፍ ደረጃ የእጅ መታጠብ እና የመፀዳጃ ቤት ቀኖች ይከበራሉ፡፡ በዚህ ዓመት የመፀዳጃ ቤት ቀን የውሀ አቅርቦት እና ሳኔቴሽን ትብብር ካውንስል ፣ ኤስ ኤን ቪ የኔዘርላንድ የልማት ድርጅት ከጤና ጥበቃ ከሀይጅን እና አካባቢ ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር  ህዳር 10 ቀን የጤና ጥበቃ ሚኒስተሬ ዲኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በተገኙበት ተከብሯል፡፡ በዕለቱ የተነሱተን ዋና ነጥቦች ለማስታወስ ያህል- በኢትዮጵያ 27 ሚሊዮን ዜጎች ሜዳ ላይ ይፅዳዳሉ፡፡ በሀገረቱ ከሚከሰቱ ህመሞች 30 በመቶ የሚሆኑ ተላላፊ በሽታዎች መንስኤያቸው ከመፀዳጃ ቤት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ተላላፊ በሽታዎች በመጨመራቸው በየዓመቱ ከ13 ቢሊዮን በላይ ብር ለመድሀኒት ግዥ እና ለሌሎች ህክምና ወጪዎች ይወጣል፡፡ ከከ10 ዓመት በፊት መፀዳጃ ቤት የሚጠቀሙ ዜጎች ቁጥር 40 በመቶ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ግን 70 በመቶ ደርሷል፡፡ የገጠሩ የሀገሪቱ ክፍል  ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት በፍጥነት ነፃ እየሆነ ቢመጣም የሚሰሩት መፀዳጃ ቤቶች የተሻሻሉ አይደሉም፡፡  
ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮቸ ለመቅረፍ በሀገር ደረጃ ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያተኮሩ ፓሊሲዎች ተቀርፀዋል፤ ተቋማዊ አደረጃጀቶች ተፈጥረዋል፡፡ የዋን ዋሽ ሀገር አቀፍ ፕሮግሮም ለዚህ ተጠቃሽ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የንፅህና አገልግሎት ፍላጎት እና አቅርቦት  ዙርያ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ የተሻሻለ መፀዳጃ ቤት መገንባት፣ ማዳ ላይ መፀዳዳትን ማስቀረት፣ ጤናማ የድረቅ እና ቆሻሻ አወጋገድ ላይ የተቀናጀም አሰራር በመተግበር ለ2020 የምናደርገውን የንፅህና ጉዞ የተሳካ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚረዳ ፅዱ ኢትዮጵያ የተባለ ሀገራዊ ሰነድ በ2012 ዓም ህዳር ወር በተደረገው የውሃ እና ሳኒቴሽን ባለድርሻ አካላት ፎረም በተከበሩ ዶ/ር አ/ር ስለሺ በቀለ የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር  ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
አዎ! ዋናው ነገር ጤና፤ የጤና መሰረቱ ንፅህና! ሁሉንም ለማሳካት እንድ መሰረታዊ ነገር ያስፈልጋል- እርሱም የባህሪ ለውጥ፡፡ ይመለከተኛል ማለት ምክንያቱም ጉዳዩ የእኔም፣ የአንተም፣ የሁላችንም ነውና፡፡     


              ይህ ፅሁፍ በውሀ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ትብብር ካውንስ እና ኤስ ኤን ቪ የኔዘርላንድ ልማት ድርጅት ስለ ውሀ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ግነዛቤ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡


Read 3217 times
Administrator

Latest from Administrator