ድረገጹ በየወሩ በአማካይ 92.5 ቢሊዮን ጊዜ ተጎብኝቷል
ታዋቂው የመረጃ ፍለጋ አውታር ጎግል በአመቱ በብዛት በመጎብኘት ቀዳሚው የአለማችን ድረገጽ ለመሆን መብቃቱና ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 ድረገጹ በየወሩ በአማካይ 92.5 ቢሊዮን ጊዜ መጎብኘቱ ተዘግቧል፡፡
በየአመቱ ከ2 ትሪለዮን በላይ የመረጃ ፍለጋ ጥያቄዎችን የሚያስተናግደውንና የጎብኝዎቹ ቁጥር ካለፈው አመት የ52.9 በመቶ እድገት ያሳየውን ጎግል በመከተል ዩቲዩብ 34.6 ቢሊዮን ጊዜ በመጎብኘት፣ ፌስቡክ ደግሞ 25.5 ቢሊዮን ጊዜ በመጎብኘት የሁለተኛና የሶስተኛ ደረጃን መያዛቸውን ቪዡዋል ካፒታሊስት ድረገጽ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
ባየወሩ በአማካይ ትዊተር 6.6 ቢሊዮን፣ ዊኪፔዲያ 6.1 ቢሊዮን፣ ኢንስታግራም 6 ቢሊዮን፣ ባይዱ 5.6 ቢሊዮን፣ ያሁ 3.8 ቢሊዮን፣ ኤክስቪዲዮስ 3.4 ቢሊዮን፣ ፖርንሃብ 3.3 ቢሊዮን ጊዜ ያህል በመጎብኘት ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውንና በብዛት ከሚጎበኙ 50 ታዋቂ የአለማችን ድረገጾች መካከል 27ቱ መቀመጫቸው በአሜሪካ መሆኑንም መረጃው አክሎ ገልጧል፡፡